ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ በአረንጓዴ ትራንስፖርት (Green Mobility ) ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

News news
2025-09-29 08:43:26

መስከረም  19/2018 ዓ.ም (ትሎሚ)፡- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ  ከአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ እና   ከደብረ ብርሃን  ዪኒቨርስቲ  ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሰማረ መለሰ ጋር  በአረንጓዴ ትራንስፖርት በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከራካሪዎች ዙሪያ በጋራ ለመስራት  ስምምነት ፈርመዋል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ  ሚኒስትር  ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ  ከምርምር ተቋማት ጋር መስራት ለተቋሙ ዘርፈ ብዙ  ጠቀሜታዎች  እንዳለው ጠቅሰው  ኢትዮጵያ የጀመረችውን የአረንጓዴ ትራንስፖርት እውን ለማድረግ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር እና  በቅርበት  መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ባረኦ ሀሰን በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ የተሽከርካሪ ስታንደርድ ከማውጣት ጀምሮ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በሰራቸው ስራዎች ላደረጉት ሙያዊ እገዛ ያመሠገኑ ሲሆን ስምምነቱ ስራዎችን ይበልጥ ለማስፋፋት አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ስምምነቱ የኤሌክትሪክ መኪኖች ጋር በተያያዘ  ትግበራ፣መሠረተልማትን ማስፋፋት፣የመረጃ ስርዓቱን በጥናት እና ምርምር ማገዝ፣አመታዊ እና ወቅታዊ ሁነቶችን በጋራ ማዘጋጀት ፣የተሽከርካሪ ስታንዳርድ ትግበራ፣ የባትሪ አያያዝ እና አወጋገድ ፣ የሰው ሀበት ልማት እንዲሁም የማህበረሰብ ግንዛቤ መፍጠር ላይ ጥናት እና ምርምር በማድረግ ኢትዮጵያ በቀጠናው ያላትን መሪነት ይዛ እንድትቀጥል በጥናት  እና ምርምር የተደገፈ ስራ በጋራ  መስራት ያስችላል ብለዋል።

የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ በበኩላቸው የአሁኑ ሰምምነቱ  ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ከዚህ በፊት ሲሰሩ የነበሩ ስራዎችን የበለጠ ሊጠናክር  የሚያስችል ነው ያሉ ሲሆን ሀገር ውስጥ ያሉ ችግሮችን  ለመፍታት  ዩኒቨርስቲው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን  ጠቁመዋል፡፡ 

የደብረ ብርሃን  ዪኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሰማረ መለሰ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ  በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ዙሪያ  ዪኒቨርስቲው  ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ስምምነቱም የበለጠ ትኩረት ሰጥተን እንድንሰራ ያስችላል ብለዋል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃዎችን ለማግኘት

556718442_1125303663108844_4300682499398737801_n-(1)-223226.jpg 557170975_1125303946442149_4477652429860665020_n-752191.jpg 557574729_1125303899775487_1969013538932945697_n-489160.jpg 557627539_1125303859775491_8905484452718583993_n-944618.jpg 556865008_1125303756442168_2622379201395779998_n-567549.jpg 555647998_1125303703108840_3599823654626825173_n-376674.jpg 555547850_1125303583108852_8227404003229884599_n-839341.jpg